በኢትዮጵያ መንግስት እና በኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ግንባር መካከል የሰላም ስምምነት ተፈረመ።

ጥቅምት 242009, (GCDC) - የኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ግንባር የኢፌዲሪን ሕገመንግስት በመጻረር የትጥቅ ትግልን አማራጭ አድርጎ ሲታገል ቆይቷል።

 ግንባሩ 2004 . ጀምሮ ከመንግስት ጋር የተለያዩ ውይይቶችን አድርጎ የትጥቅ ትግል አማራጩን በመተው በሰላማዊ መንገድ ለመታገልና ሕገመንግስታዊ ስርዓቱን በመቀበል ለመንቀሳቀስ እና ለኢትዮጵያ ሔራዊ ጥቅም ለመቆም መወሰኑን ገልጿል።

ስምንት ነጥቦች ያሉት የሰላም ስምምነትም ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር ተፈራርሟል።

የመከላከያ ሚንስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ በትጥቅ ትግል ውስጥ የነበሩ የተለያዩ ድርጅቶችና ቡድኖች በሰላማዊ መንገድ እየገቡ መሆናቸውን ገልጸው የኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ግንባርም የዚሁ አካል ነው ብለዋል።

 መንግስት የትጥቅ ትግል አማራጭን በመተው በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ የሚፈልጉ አካላትን ለመቀበል ሁሌም ዝግጁ መሆኑንም የመከላከያ ሚንስትሩ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ግንባር ሊቀመንበር አቶ ቱዋት ፖል ቻይ ከጦርነት ምንም የሚገኝ ነገር ስለሌለ ወደ ሰላማዊ አማራጭ መምጣታቸውን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ለሰላማዊ ትግል የተመቸ በመሆኑ አባሎቻቸውን ወደ አገር ውስጥ በማስገባት በሰላማዊ መንገድ እንደሚታገሉም ገልጸዋል።

ሪፖርተር:- ተስፋዬ አባተ Source: EBC